

<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<feed xmlns="http://www.w3.org/2005/Atom" xml:lang="am">
                        <id>https://eeu.gov.et.bornatol.com/feed/am</id>
                                <link href="https://eeu.gov.et.bornatol.com/feed/am" rel="self"></link>
                                <title><![CDATA[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት RSS Feeds]]></title>
                            
                                        <subtitle>ይህ RSS feed በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ድረገጽ(https://www.eeu.gov.et) ላይ የታተሙ ይዘቶችን ይዟል.</subtitle>
                                                    <updated>2026-04-18T08:31:24+03:00</updated>
                        <entry>
            <title><![CDATA[በመሰረተ ልማትና በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተመዘገበው ዕድገት ለቀጣይ የአገሪቱ ብልፅግና መረጋገጥ መሰረት የሚጥል ነው - የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ም/ጠቅላይ ሚኒስትር]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et.bornatol.com/news/detail/2218?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et.bornatol.com/2218</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p style="text-align:justify;">የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን ጨምሮ በአገር አቀፍ ደረጃ በመሰረተ ልማትና በኮንስትራችሽን ዘርፍ የተሰማሩ ታላላቅ ተቋማት የሚሳተፉበት የኢትዮጵያ መሰረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሳምንት በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል ዛሬ በደማቅ ስነ ስርዓት ተከፈተ፡፡ &nbsp;</p><figure class="image image_resized image-style-align-right" style="width:75%;"><img src="https://www.eeu.gov.et/lfm/1776490234.jpg" srcset="https://www.eeu.gov.et/lfm/1776490234.jpg 800w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1776490234.jpg 1024w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1776490234.jpg 1920w" sizes="100vw" width="1920"></figure><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">መርሃ ግብሩን የከፈቱት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እንደገለፁት በአገራችን በመሰረተ ልማትና በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተመዘገበው ዕድገት ለቀጣይ የአገሪቱ ብልፅግና መረጋገጥ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">መሰረተ ልማት ለአንድ ሀገር የደም ስር መሆኑን የገለፁት ም/ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስት ከመሰረተ ልማት ግንባታ ወደ ስርዓት ግንባታ እየተሸጋገረ መሆኑን አብራርተዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">አክለው ባለፉት ሁለት አመታት 182 ሺ ኪ.ሜ የመንገድ፣ ከአንድ መቶ ሺ በላይ የኤሌክትሪክ መስመር፣የአውሮፕላን ማረፊያ፣ የቴሌኮም መሰረተ ልማትና አገልግሎት ማስፋፊያ፣ ሰፋፊ የመስኖ ግንባታዎች መከናወናቸውን ገልፀው ይህም ዲጂታል ኢትዮጵያን 2030 ዕውን ለማድረግ መሰረት የሚጥል መሆኑን ተናግረዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ዛሬ በተከፈተው አውደ ርዕይ ላይ ለዕይታ የቀረቡት መሰረተ ልማቶች አገራችን እያስመዘገበች ያለውን ዕድገት የሚያመላክት ነው ብለዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">የከተማ መሰረተ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው ዛሬ የተከፈተው የመሰረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሳምንት የአገራችንን ብልፅግና የምንመዝንበት እና የዘርፉን ቀጣይ ዕድገት የሚያመላከት ስትራቴጂ የሚቀመጥበት መሆኑን ገልፀዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ዘርፉ ለአገሪቱ የኢኮኖሚው ሽግግር የጀርባ አጥንት መሆኑ በመንግስት በኩል የሚታመንበት በመሆኑ በአሁኑ ወቅት ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በአጭር ጊዜ ማጠናቀቅ ባህል እየሆነ መምጣቱንና ዘርፉንም በዲጂታል ስርኣት እንዲመራ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በአገር አቀፍ ደረጃ የመሰረተ ልማት ተቋማት በቅንጅት መስራት በመቻላቸው ከፍተኛ ሀብት ከብክነት ማዳን መቻሉንም ገልፀዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ዛሬ የተጀመረው የመሰረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሳምንት ለሚቀትሉት ሶስት ቀናት ለጎብኝዎች ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን የመሰረተ ልማትና እና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎች አቅርበው ሰፊ ውይይት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-04-18T08:31:24+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[በኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ከ12 ሺህ በላይ ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑ]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et.bornatol.com/news/detail/2216?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et.bornatol.com/2216</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p style="text-align:justify;">በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን በኮዬ ፈጬ ኮንዶሚንየም ፕሮጀክት 11 እና 18 የሚኖሩ ከ12 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረጉን አስታወቀ፡፡</p><figure class="image image_resized image-style-align-right" style="width:75%;"><img src="https://www.eeu.gov.et/lfm/1776412225.jpg" srcset="https://www.eeu.gov.et/lfm/1776412225.jpg 800w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1776412225.jpg 1024w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1776412225.jpg 1920w" sizes="100vw" width="1920"></figure><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ነዋሪዎቹን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ 17.3 ኪ.ሜ የዝቅተኛ ቮልቴጅ መስመር፣ የ8.4 ኪ.ሜ የመካከለኛ ቮልቴጅ የመሬት ውስጥ ተቀባሪ መስመርና የ4.1 ኪ.ሜ የመካከለኛ ቮልቴጅ የአየር ላይ መስመር ዝርጋታ ተከናውኗል፡፡ &nbsp; &nbsp;</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በተጨማሪም 11 ባለ 630 ኬ.ቪኤ ትራንስፎርመሮች፣ 21 ባለ 800 ኬቪኤ እንዲሁም 21 ባለ 1250 ኬቪኤ ትራንስፎርመሮች በአጠቃላይ 53 ትራንስፎርመሮች እንዲተከሉ ተደርጓል፡፡ በተያያዘ ለነዋሪዎቹ 12 ሺህ 100 ቆጣሪዎች ተገጥመዋል፡፡ &nbsp;&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ነዋሪዎቹ ከዚሀ በፊት በየ ብሎኩ በተገጠመ ባለ ሶስት ፌዝ ቆጣሪ በጋራ ይጠቀሙ የነበረ ሲሆን፤ በዚህም በኃይል ማነስና መቆራረጥ ሲቸገሩ ቆይተዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በአሁኑ ወቅት በተናጠል ቆጣሪ እንዲገጠምላቸው በመደረጉ ከ12 ሺህ በላይ ነዋሪዎች በቂ ኃይል እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፡፡</p><p style="text-align:justify;">ሪጅኑ የመስመር ዝርጋታውን በሚያከናውንበት ወቅት ተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ስርቆት ማጋጠሙ የተጠቀሰ ሲሆን በአንፃሩ የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ዝርጋተው በወቅቱ እንዲጠናቀቅ ነዋሪዎች ከፍተኛ ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸው ተጠቁሟል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በቀጣይ በአዲስ አበባ ቤቶች በኩል የሚፈፀሙ ክፍያዎች እንደተጠናቀቁ በኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም በተለያዩ ሳይቶች የሚገኙ ነዋሪዎችን በተናጠል የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የማድረግ ሥራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ ይሆናል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-04-17T11:35:59+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[የኃይል አጠቃቀም ግንዛቤ ማስጨበጫ መድርክ ተካሔደ]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et.bornatol.com/news/detail/2215?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et.bornatol.com/2215</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p style="text-align:justify;">የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞች በኃይል አጠቃቀም እና ቁጠባ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ፡፡ &nbsp; &nbsp;</p><figure class="image image-style-align-right image_resized" style="width:75%;"><img src="https://www.eeu.gov.et/lfm/1776411905.jpg" srcset="https://www.eeu.gov.et/lfm/1776411905.jpg 800w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1776411905.jpg 1024w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1776411905.jpg 1920w" sizes="100vw" width="1920"></figure><p style="text-align:justify;">የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ የተካሄደው ከቂርቆስ &nbsp;ክ/ከተማ ለተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ሲሆን ደንበኞች በተለይም በቤት ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል በመጠቀም የሚያከናውኗቸውን ተግባራት እንዴት ኃይል ቆጣቢ በሆነ መንገድ ማከናወን እንዳለባቸው ትምህርት ለመስጠት የሚያስችል ነው፡፡ &nbsp;</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ደንበኞች የተጋነነ የፍጆታ ሂሳብ እንዳይኖር ለማድረግ፣የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ፣ የከባቢ አየር ንብረት ለውጥን ለመጠበቅ እና ኢነርጂ ለሁሉም ማህበረሰብ ለማዳረስ እንዲሁም የኃይል አጠቃቀማቸውን በማስተካከል አስተዋጽኦ እንዲያደርጉም ጥሪ ቀርቧል፡፡ &nbsp;</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በመድረኩ ደንበኞች ከእውቀት ማነስ እና ከቸልተኝነት በሚመነጩ ተግባራት የሃይል ብክነት እንደሚፈፅሙ የተገለፀ ሲሆን እነዚህን ተግባራት ለማረም ኃይል ቆጣቢ የኤሌክትርክ ቁሳቁሶችን መጠቀም፣የኤሌክትሪክ ሶኬቶችን በማይጠቀሙበት ጊዜ ማጥፋት፣ ጥራት ያላቸውን የኤሌክትርክ ቁሳቁሶችን መጠቀም እና መሰል ተግባራትን መለማመድ እንደሚገባ ተጠቁመዋል፡፡ &nbsp;<br>&nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp;<br>ከኃይል አጠቃቀም በተጨማሪ ደንበኞች የኃይል እና የመሰረተ ልማት ስርቆትን በመከላከል ንብረትን በመጠበቅ እና በመቆጣጠር የበኩላቸውን ሃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ በመድረኩ ላይ ተነስቷል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ዛሬ የተጀመረው የኃይል አጠቃቀም እና የኢነረጂ ቁጠባ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነገም የሚቀጥል ይሆናል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-04-17T10:45:39+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[ከ6ሺህ በላይ ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑ]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et.bornatol.com/news/detail/2213?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et.bornatol.com/2213</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p>የአርባምንጭ ሪጅን በአከናወነው የማስፋፊያና የመልሶ ግንባታ ሥራ 6ሺህ 200 ነዋሪዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረጉን የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ገረመው ወንድምሁነኝ ገለፁ፡፡</p><p>&nbsp;</p><p>ዳይሬክተሩ እንደገለጹት የኤሌክትሪክ ተደራሽነት እውን ለማድረግ 14.5 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር እና 18 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር የተዘረጋ ሲሆን 5 ትራንስፎርመሮችም ተተክለዋል፡፡&nbsp;</p><figure class="image image_resized" style="width:75%;"><img src="https://www.eeu.gov.et/lfm/1776330108.jpg" srcset="https://www.eeu.gov.et/lfm/1776330108.jpg 800w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1776330108.jpg 1024w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1776330108.jpg 1920w" sizes="100vw" width="1920"></figure><p>ይህም በአካባቢው የሚስተዋለውን የኃይል መቆራረጥ ችግር &nbsp;ለመፍታት እና የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ተጠቅሷል፡፡ &nbsp;<br>&nbsp;<br>በተጨማሪም ሪጅኑ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድርግ 7.24 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር ላይ የመልሶ ግንባታ ሥራ እንዲከናወን መደረጉ ተጠቁሟል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አምስት ትራንስፎርመሮች ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራ በመከናወኑ የኃይል አቅርቦት አስተማማኝ እንዲሆን መደረጉ ተጠቅሷል፡፡</p><p>&nbsp;</p><p>አርባምንጭ እንደ ቱሪዝም መዳረሻ ከተማ እንደመሆኗ ቁልፍ ደንበኞችን፣አምራች ኢንዱስትሪዎችን እና የንግድ ተቋማትን በተለየ ትኩረት በመስጠት አገልግሎቱን በማሻሻል እያገለገለ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡</p><p>&nbsp;</p><p>በዚህም የካሳቫ ፋብሪካ፣ የውኃ መሳቢያ ፕሮጀክቶች፣የ“ገበታ ለትውልድ” አርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት፣ ሆቴሎች፣ የጫጩት ማስፈልፈያ ማዕከላት፣የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ተቋማት፣ ወፍጮዎች እና ሌሎች ተቋማት የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል፡፡&nbsp;<br>&nbsp;<br>እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ እነዚህ ሥራዎች በከተማው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዲበረታታ ብቻ ሳይሆን በቱሪዝም ዘርፍ ያለውን እድገት ለማጠናከር እና የሥራ ዕድሎችን ለማፍጠን &nbsp;አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ተጠቁሟል፡፡</p><p>&nbsp;</p><p>በቀጣይም የኤሌክትሪክ ተደራሽ ባልሆነባቸው አካባቢዎች ለማስፋፋት እና ያለውን አገልግሎት ለማሻሻል በተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡<br>&nbsp;</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-04-17T10:36:46+03:00</updated>
        </entry>
    </feed>
